ገፆች

ዓርብ 20 ኤፕሪል 2018

ምን ያህል ውሃ (እንዲሁም ምግብና ሌሎች ንጥረ ነገሮችን) መውሰድ አለብን? - የመረጃዎቹ ሳይንሳዊ መሠረት

ሲ ኤን ኤን (CNN) በቅርብ ጊዜ በድረ ገጹ ላይ (http://edition.cnn.com/2017/09/27/health/benefits-of-water-and-fluids/index.html) እንዲሁም ሌሎች የውጭ እና የሃገር ውስጥ የሚዲያ አውታሮች በቀን ውስጥ ምን ያህል ውሃ መጠጣት እንደሚኖርብን ሲነግሩን፣ ወንዶች 3.7 ሌትር በቀን ሴቶች ደግሞ 2.7 ሌትር በቀን እንደሆነ ይመክሩናል። ለዚህም መረጃ መነሻው የአሜሪካው የሳይንስ የምህንድስናና የህክምና ምርምር ተቋም (The National Academies of Science Engineering and Medicine) የውሃና የተለያዩ ለሰውነታችን የሚያስፈልጉ ንጥረ ነገሮችን የምንወስድበት መጠን ከሚገልጸው ህትመት (Dietary Reference Intakes: Water, Potassium, Sodium, Chloride and Sulphate - https://www.nap.edu/read/10925/chapter/1) ሲሆን፣ ጠለቅ ብለን ጉዳዩን ስንመለከት ግን መውሰድ ያልብንን የውሃ መጠን መወሰን በሚዲያዎቹ እንደተገለሰው ያህል ግልጽ አለመሆኑን እንረዳለን።
የውሃውን መጠን ጉዳይ ከመመልከታችን በፊት ግን በጥቅሉ ለጤናችን የሚያስፈልጉን የተለያዩ የምግብና የመጠጥ መጠኖችን እንዴት ነው ማወቅ ወይም መገመት የምንችለው? ይህን ለመመለስ በሳይንሳዊ ሂደት ምን ዓይነት ጥናቶችን መተግበር እንደምንችልና ከጥናቶቹ የሚገኙ መረጃዎች አስትማማኝነትን በዚሁ ህትመት በመጠኑ ተብራርተዋል።
በመጀመሪያ ደረጃ የተጠቀሰው በላብራቶሪ እንሰሳት ላይ የሚደረግ ጥናት ሲሆን፣ የዚይ ዓይነት ጥናት ጥንካሬው በረቀቀ ሁኔታ ለእንሰሳቱ የሚሰጡትን የምግብና የንጥረ ነገሮችን መጠኖች መቆጣጠር ሲቻል፣ እንዲሁም ከእንሰሳቶቹ ዘር ጾታ ወይም አካባቢያዊ ለዩነቶች በጥናቱ ልይ ሊኖራቸው የሚችለውን ተዕጽኖ በአግባቡ መለየት ያስችላል። በሌላ ጎኑ ግን እንሰሳትና ሰው የስውነት ትግባራቶቻቸው ላይ ልዩነቶች በመኖራቸውና፣ ላብራቶሪ ውስጥ ልናገኛቸው የምንችለው ጥብቅ የሙከራ ሁኔታዎች በነጻነት ወይም በተፈጥሮአዊ ሁኔታ ለሚኖሩት ሙሉ ለሙሉ አመላካች ሊይሆኑ አለመቻላቸው የገኛሉ።
በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠውን ስንመለከት፣ በጥናት ማዕከል ውሰጥ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች የሚመገቡትን በመመጠንና በመቀያየር የሚሠራ ጥናት ነው። የተለያዩ አመጋገብ ዙሪያ የምናገኛቸው መረጃውች አብላጫዎቹ በዚህ ዓይነት የተገኙ ሲሁን የህም የጥናት ዓይነት የራሱ ድክመቶች ይኖሩታል። እነዚህም በሰው ላይ የሚሠሩ ጥናቶች ለውስን ጊዜ ስለሚካሄዱ በረጅም ጊዜ የአመጋገብ ባህረዮች ያለቸውን ጥቅምና ጉዳት መገመት አለማስቻል፣ ጥናቱ ላይ የሚሳተፉት አነስተኛ ቁጥር ከመሆኛቸው ውጤቱ ላይ የሚኖረን መተማን ደረጃ የመቀነስና እንዲሁም በጥናት ማዕከል ውስጥ የሚሠራው ምን ያህል ቀን እስተቀን ኑሮውን ወደሚያካሂደው በቀትታ አመላካች መሆን አለመቻሉ ይገኙበታል።
ሶስተኛው የጥናት ዓይነት የለት ተለት ኑሮዋቸውን እያካሄዱ ያሉ የሀብረተሰቡ አባላትን በመመልከትና የተለያዩትን አመጋገብ ባህርይዮች በህብረተሰቡ ከሚታዩ የጤና ጉድለቶች ጋር ለማዛመድ መሞከር ሲሆን፣ የዚህ ዓይነት ጥናት ችግር የታዩት የአመጋገብ ባህርዮች በቀጥታ የጤና ጉድለቶቹን ለማስከተላቸው ወይስ ከሌላ ግምት ካልተሰጣቸው ወይም ከተደበቁ ነባራዊ ሁኔታዎች የተከተሉ ለመሆናቸው እርግጠኛ መሆን አለመቻል ነው። ብዚህ አይነት የተገኘ መረጃን ለማጠናከር የተለያዩ ህብረተሰቦችን ደጋግሞ ማጥናትና የጥናቱ ተሳታፊዎች ማብዛት መፍትሄ ሊሆን ይችላል።
አሁን ግን ወደ ውሃው ጉዳይ ስንመለስ ጽሁፉ የሚነግረን በአሜሪካ ውስጥ የሚገኙ ከ19 እስከ 30 ዓመት ዕድሜ ያሉ ውንድና ሴት የህብረተሰብ አባላት ለተላከ መጠየቂያ ምላሾች ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ እነዚህ አባላት የሚጠጡት አማካይ የውሃ መጠን ለአብዛኛው ሰው በቂ ይሆናል ተብሎ ስለሚገመት ነው። ጽሁፉ በዙ የሚንቀሳቀሱ ወይም መቆታማ አካባቢ ያሉ ከተጠቀሰው መጠን የበለጠ መውሰድ ሊኖርባቸው እደሚችልም ይገልጻል።
ነግር ግን የአሜሪካውን በቀጥታ ለራሳችንም እንደሚሆን መቀበል አለብን ወይ? በአንደኛ ደረጃ ከአሜሪካው የሚለየን አማካይ የሰውነታችን ክብደት ሲሆን፣ የአመሪካው 80.7 ኪሎግራም ሲሆን የኛ ደግሞ 60.7 ኪሎግራም ነው። ከዚህ ብቻ ተነስተን የተጠቀሱትን ቁጥሮች 75 ከመቶ በመቀነስ ለወንዶች 2.8 ለሴቶች ደግሞ 2.0 ሌትር ይሆናል ማለት ነው። ሌላው መገንዘብ ያለብን የተጠቀሱት ቁጥሮች በመጠጣት ብቻ ሳይሆን ከምግብም የምናገኘውን ውሃ ያጠቃለሉ እንደሆኑና ብዙ የምንመገባችውም ከፍተኛ የውሃ ይዘት ይንዳላቸው ነው። ለምሳሌ ዳቦ 40 ከመቶ ስጋ ከ55 እስከ 77 ከመቶ እንቁላል እንደአሠራሩ 63 እስከ 75 ከመቶ አትክልትና ፍራፍሬ እስከ 97 ከመቶ ይገኙባቸዋል። ስለዚህም በቀን ውስት የተመገብነውን ግምት ውስጥ በማስገባት በውሃ መልክ የምንወስደውን መመጠን እንችላለን ።

ለማጠቃለል በዚህ ልትፍ ለማስተላለፍ የሞከርኩት አመጋገብን በተመለከተ ምንም የማያወላውል መቶ በመቶ እርግጠኛ የሆነ መርረጃ ማግኘት በጣም ከባድ መሆሁንና፣ በሚዲያ የሚተላለፉ ምክሮች በርካታው ደካማ፣ አጠያያቂ ወይም ስተታማ ሳይንሳዊ መረጃ ላይ የተመሠረቱ ሊሆኑ እንደሚችል በመገንዘብ፣ በጥርጣሬ ዓይን መመልከት እንደሚኖርብንና ከነዘኢህ መረጃ ተነስተን በኑሮዋችን ለይ በምናረግው ለውጥ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግው ነው።  

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ