ገፆች

ማክሰኞ 25 ፌብሩዋሪ 2025

ረቂቁ አቶም 4ሐ– ኤንዛይም ምንድነው

 

ኤንዛይሞች በሁሉም ፍጡሮች ውስጥ የሚገኙ እጅግ አስገራሚ ፕሮቲን ውህዶች ናቸው። ኤንዛይሞች አንድን ውህድ ከፋፍለው ወደ ሌሎች መጠናቸው ያነሱ ውህዶች፣ ወይም አነስተኛ ውህዶችን ገጣጥመው ተለቅ ወዳለ ውህድ የመቀየር ችሎታ አላቸው። ለምሳሌ ግልይኮጅን ሲንቴዝ (glycogen synthase) ሰውነታችን ለሃይል የሚጠቀምበትን ግሉኮዝ (glucose) የተባለውን ውህድ ሰውነታችን ከሚያስፈልገው መጠን በላይ ሲሆን፣ ሃይልን ለማጠራቀም ወደሚያስችልው ግላይኮጅን (glycogen) ወደተባልው፣ ብዛት ያላቸውን የግሉኮዝ ውህዶችን ቀጣጥሎ በተለያዩ ይሰውነት ክፍሎቻችን ለሌላ ጊዜ ለማከማቸት ወደሚያስችለን መልክ ይቀይራል። በተቃራኒው ግላይኮጅኔዝ (glycogenase) የግሉኮዝ እጥረት ባለ ጊዜ ግላይኮጅንን መልሶ ወደ ግሉኮዝ በመቀየር ለሃይል ማመንጫነት እንዲያገለግል ያበቃዋል። ኤንዛይሞች ተግባሮቻቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜ በራሳቸው ላይ ምንም ለውጥ የማያስከትል በመሆኑ አንዱ የኤንዛም ውህድ መልሶና መላልሶ ሥራውን በተደጋጋሚ መፈጸም ይችላል። ይህን የመሰሉ ተግባራትን የሚፈጽሙ ወደ 75000 የተለያዩ ኤንዛሞች በሰውነታችን ይኖራሉ ተብሎ ይገመታል። ከዚህ በፊት በነበረው ልጥፍ የተመለከትነው አንጂዮ ቴንሲን ኮንቨርቲንግ ኤንዛይምም (Angitensin Converting Enzyme) ከንዚህ አንዱ ነው። ኤንዛይሞች በአባዛኛዎቹ የሰውነታችን ተግባራት ሚና ስለሚኖራቸው ከላይ እንዳየነው የተለያዩ ዘመናዊ መድሃኒቶችም እነሱን ኢላማ ያሚያደርጉ ናቸው። እነዚህ ድንቅ ፕሮቲን ውህዶች ከሚፈጽሟቸው ተግባርፕች መሃል የምንመገባቸውን ምግቦች መፍጨት፣ ሰውነታችንን መገንባት፣ ወደሰውነታችን የገቡ አደገኛ ንጥረ ነገሮችን (መርዞችን) ማምከን የመሳሰሉት ይገኛሉ። ቀደም ሲል ከተመለከትነው የደም ብዛት በተጨማሪ አንድ ሁለት ምሳሌዎችን ብንመለከት፣ አንዳንድ ወተት የማይስማማቸው ሰዎች ወተት ውስጥ የሚገኘውን ላክቶዝ (lactose) የተባለ ይስኳር አይነትን ወደ ሃይል ሰጭው ግሉኮዝ የሚቀይረው ላክቴዝ (lactase) የተባለ ኤንዛይም እጥረት ሲኖራቸው፣ የጨጓራ ህመም ያላቸው ደግሞ ፕሮቶን ፓምፕ (proton pump) የተባለው ኤንዛይም ከልክ ያለፈ አሲድ እንዲመረት የሚያደርግ ሲሆን፣ የህንንም ተግባሩም የሚከለክሉ ፕሮቶን ፓምፕ ኢንሂቢተር (proton pump inhibitor) የተባሉ መድኅኒቶችን (ለምሳሌ ኦሜፕራዞል – omeprazole) በመጠቀም ህመሙን ለመከላከል እንችላለን።

ሰኞ 20 ጃንዋሪ 2025

ረቂቁ አቶም (ክፍል 4ለ) - ካፕቶፕሪል (Captopril) የደም ብዛት መድሓኒት

 

በርካታ በሰውነታችን የሚገኙ ውህዶች የደም ግፊት መጠን ላይ ተዓጽኖ አላቸው። ለምሳሌ በምንጨነቅበት ጊዜ የተለያዩ ዓጢዎች የሚያመነጯቸው ውህዶች ወይ የልብ ትርታ ፍጥነትን በጨመር፣ ወይ የደም ሥር ስፋትን በመቀነስ፣ ወይ የሚዘዋወረውን የደም መጠን በመጨመር የደም ግፊታችንን ከፍ ሊያረጉ ይችላሉ። አንዳንድ ክስተቶችም የደም ግፊት መጠንን ሊቀንሱ ይችላሉ። ለምሳሌ የደም ኢንፌክሽን የትናንሽ የደም ስሮችን ስፋት በመጨመር ይህንን ሊያስከትል ይችላል። በአጠቃላይ የደም ግፊት መጠን ከልክ በላይ መጨመር ወይም መቀነስ ሰውነታችን ላይ አሉንታዊ ተዓጽኖ የሚያስከትል ሲሆን፣ አንዳንድ ጊዜ ግን መሠረታዊ መንስኤዎቹ ግልጽ ላይሆኑ ይችላሉ። በጉልምስና ጊዜ አንዳንድ ሰው ላይ የሚታየውም አብዛኛውን ጊዜ መንስኤው በግልጽ ባይታወቅም፣ በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ውህዶች መጠን መዛባት እንደሚኖር መገንዘብ ተችሏል። ከነዚህም አንድ ምሳሌ ቀጥለን እንመለከታለን።

እንደ አውራፓውያን አቆጣጠር በ1960ዎቹ የእባብ መርዝ ውስጥ የሚገኝ ፔፕታይድ (peptide) የተባለ ውህድ በሰውነታችን ውስጥ በተፈጥሮ የሚገኘውን ኤስ (ACE – Angiotensin Converting Enzyme) የተባለ ውህድን ሥራ እንደሚያስተጓጉል በእንግሊዝ ያሉ ሳይንቲስቶች ሊይስተውሉ ቻሉ። ኤስ ኤንዛይም ተብልው ከሚጥሩ በርካታ የፕሮቲን ይዘት ካላቸው ውህዶች አንድ ሲሆን፣ በ1970ዎቹ ኤስ አንጂዮቴንሲን አንድ (Angiotensin 1) የተባለውን ውህድ ወደ አንጂዮቴንሲን ሁለት (Angiotensin 2) ወደሚባለው በመቀየርና ይህም ኩላሊት ላይ ባልው ተዓጽኖ በደም ስሮቻችን የሚዘዋወረውን የደም መጠን በመጨመር የደም ግፊትን ከፍ እንደሚያደርግ ተስተዋለ። ይህን ተከትሎ በ 1975 የእባብ መርዝ ውስጥ የሚገኝውን ፔፕታይድ የሚገኙትን የአቶሞች ዓይነቶችና ቅርጹንም በመረዳት ተመሳሳይ ውህድ በላብራቶሪ ውስጥ ካፕቶፕሪል (Captopril) የተባለ ውህድ በኮምፒዩተር በመታገዘ ዲዛይኑን መንደፍና ቀጥሎም ማምረት ተቻለ። የኤስና የካፕቶፕሪል ጥምር ቅርጽ ካታች እንደምንመለከተው ይምስላል። ካፕቶፕሪል የውህዶችን ቅርጽ መሠረት አድርጎ መድሓኒትን ዲዛይን የማድረግ ተግባር የመጀመሪያ ስኬት ሲሆን ለዚህም ሥራ በዚህ ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረውን ጆን ቬይን የተባለ ሳይንቲስት በ1980ዎቹ የኖቤል ሽልማትን አስገኝቶታል።

በዚህ ምስል ይኤስ አቶሞች ውሃዋማ ሆነው ሲታዩ ከመካከሉ የካፕቶፕሪል ውህድ የአንጂዮቴንሲን አንድን ቦታ ይዞ እንመለከታለን

 

ይህ ምሳሌ የሚያሳየን የአቶሞችንና የውይዶችን ባህርይና ቅርጽ በመሠረታዊ ሳይንስ ምርምር ዘዴዎች መረዳት ዘመናዊ ህክምና ላይ ምን ያህል አስተዋጻኦ ሊኖረው እንደሚችል ያሳየናል። በአርግጥ እጅግ ብዙ በዘመናዊ ህክምና ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ መድሃኒቶች ምንም የአቶም ግንዛቤ ሳይኖረን ከልምድ የተገኙ ቢሆኑም፣ በቅርቡ ምርምር ተደርጎባቸው በአዲስ ዓይታ በሰውነታችን ላይ በምን ዓይነት የሚፈለግባቸውን ውጤት ሊፈጽሙ እንደቻሉ ማወቅ ተችሏል።

ሰኞ 2 ዲሴምበር 2024

ረቂቁ አቶም (ክፍል 4ሃ) - የደም ብዛት ህመም ምንድነው

በዚህ ልጥፍ የደም ግፊት ላይ ተዕጽኖ ያላቸውን ተቀያያሪ ነግሮችን መመልከት እንሞክራለን። በሚቀጥለው ልጥፍ የደም ብዛት ሰውናታችን ከሚገኙ ውህዶች ጋር ያለውን ግንኙነት እናያለን። የደም ብዛት ህመም ስንል በሰውነታችን የሚዘዋወረው የደም መጠን መጨመር ሳይሆን፣ በደም መዘዋወሪይ ቱቦዎች ላይ የሚከሰተው የደሙ ግፊት መጭመርን ያመለክታል። የግፊቱ መጠን በሁለት ዋና ምክኒያቶች ይወሰናል – የመጀመሪያው ልባችን የሚገፋው የደሙ መጠንና ሁለተኛው ደግሞ የደም ስሮቻችን ስፋት ወይም ጥበት ናቸው። ልባችን የሚገፋው የደሙ መጠን በተራው ሁለት ምክኒያቶች ይወስኑታል። የመጀመሪው ለባችን አንድ ጊዜ ሲመታ የሚገፋው የደም መጠንና ሁለተኛው ደግሞ ልባችን የሚመታበት ፍጥነት ነው። ይህን የበለጠ ለመረዳት ከሁሃ ፖምፕ ጋር ማነጻጸር እንችላላን። የፖምፑ ሞተር አንድ ጊዜ ሲዞር ከአንድ የልብ ትርታ፣ የፖምፑ ሞተር በደቂቃ የሚዞረው ፍጥነት ከልባችን ትርታ ፍጥነት፣ የውሃ መተላለፊያ ቧንቧዎች መጠን ደግሞ ከደም ሥሮቻችን ስፋት ይንጻጸራሉ። ስለዚህ እነዚህን ምክኒያቶች የደም ግፊት ላይ ያላቸውን ተእጽኖን ስንመለከት፣ ልብ አንድ ጊዜ ሲመታ የሚገፋው የደም መጠንና የትርታው ፍጥነት ሲጨምሩ፣ እንዲሁም የደም ሥሮቻችን ሲጠቡ የደም ግፊት እንዲጨምር ያረጉታል። ለምሳሌ የአትክልት ውሃ ማጠጫ ጎማን ስንመለከት፣ ቧንቧውን የበለጠ ስንከፍት ወደ ጎማው የሚገባው ይውሃ መጠን ይጨምርና ከጫፉ ሲወጣም የበለጠ ርቀት ይወረወራል። በርቀት የሚገኙትን ለማጠጣት ስንፈልግ ጫፉን በከፊል በጣታችን እንዘጋውና፣ ይህም በጎማው ውስጥ ያለውን ግፊት ስለሚጨምር አሁንም በበለጠ ርቀት ለማፈናጠር ያስችለናል። በጣም ቧንቧውን ከከፈትን ወይም ጫፉን ከልክ በላይ ከደፈንን ጎማው ሊፈነዳም ይችላል። በተመሳሳይ ሁኔታ የደም ሥሮቻችን ጠበው የደሙን ዝውውር ከከለከሉ፣ ደም ሥሮቻችን ሊጎዱና ሊፈነዱ ይችላሉ። በዚህ ዓይነት በአንጎላችን የሚገኙ የደም ሥሮች ሲፈነዱ ስትሮክ ተብሎ የሚጠራውን ህመም ያስከትላል። ስለዚህ ይህን ሰለ ደም ግፊት ካልን፣ ሰውነታችን ውስጥ ካሉት ውህዶች ጋር በምን ዓይነት ይገናኛል? ይህንን በሚቀጥለው ልጥፍ ከአንድ ለደም ብዛት ህመም ከሚሰት መድሃኒት አንጻር እንመለከታለን።

ረቡዕ 26 ጁን 2024

ረቂቁ አቶም (ክፍል 3ለ) - ውህዶች ምን የመስላሉ

 

አንድን ነገር ለመረዳት ስንፈልግ ካሉን ስሜቶች በከፍተኛ ደረጃ የምንጠቀመው የማየት ችሎታችንን ነው። በተጨማሪም የመስማት የመዳሰስና የመቅመስ ችሎታዎቻችንን እንጠቀማለን። ነገር ግን እንዚህ ችሎታዎቻችን በቀጥታ አቶሞችንን ለመረዳት አልጠቀሙንም። ቀደም ሲል የአቶሞችን መኖር የደረስንበት የአንዳንድ ነገሮችንን ጉልህ ባህርይ በማጥናትና፣ ቀጥለንም የማሰብና የማመዛዘን ችሎታችንን ተጠቅመን፣ እንዴት ቢሆን ነው እንዚህን ባህርዮች ሊፈጠሩ የቻሉት ብለን በመጠየቅ ነው። በዚህም ዓይነት ሁሉም ነገሮች እጅግ በጣም ረቂቅ በሆኑ አቶሞች እንደተሠሩ የደረስንበት።

አቶሞችን መመልከት የሚከለክለን ረቂቅነታቸው ብቻ አይደለም። ምንም ዓይነት እዚህ ጀምሮ እዚህ ያልቃል የምንለው ጠጣር ይዘት የላቸውም። ነገር ግን በውስን መልኩ ለመረዳት፣ አቶሞችን የተለያየ መጠን ያላችው በጣም ትናንሽ እንደ ኳስ ክብ የሆኑ አካላት መቁጠር እንችላለን። ቅጥለንም ኳሶቹን በተለያየ መንገድ በመቀጣጠል ውህዶችን ለመግለጽ መሞከር እንችላለን።

ለምሳሌ ውሃን ብንመለከት፣ አንድ የውሃ ውህድ አንድ ኦክሲጅንና ሁለት ሃይድሮጅን አቶም ይይዛል። ይህንንም እንደሚከተለው መግለጽ ይቻላል።

ውሃ

በዚህ ምስል መሃል ላይ በቀይ ኦክሲጅንን ከጎኑ ደግሞ በነጭ ሁለቱን ሃይድሮጅኖች እናያለን። ሃይድሮጅኖቹ መጠናቸው አንስ እንደሚሉና እንዲሁም ሶስቱ አቶሞች ቀጥ ባለ መስመር ላይ ሳይሆን ሸፈፍ ብለው እንደተቀመጡ እንናስተውላለን።

ሁለት ሌሎች ምሳሌዎች ፕሮፔን የተባለውን የሲሊንደር ጋዝንና በሰውነታችን የሚገኘው ግሉኮዝን ብንመለከት ፕሮፔን ሶስት ካርበንና 6 ሃይድሮጅን የያዘ ውህደት እንደሆነና፣ ግሉኮስ ደግሞ 6 ካርበን 6 ኦክሲጅንና 12 ሃይድሮጅን መያዛቸውን እናያለን።

ፕሮፔን

ግሉኮዝ

እነዚህ ምሳሌዎች አነስ ያሉ ውህዶች ሲሆኑ፣ በሰውነታችን የሚገኙት ግን በመቶዎች ወይም በሽህዎች የሚቆጥውሩ አቶሞችን ሊያካትቱ ይችላሉ። በደማችን ሂሞግሎቢን ተብሎ የሚጠራውና የደም ማነስ ሲኖርብን መጠኑ ቀንሶ የምናገኘው ፕሮቲን ከ4000 በላይ አቶሞችን ያካተተ ውህድ ሲሆን ከታች የምንመለከተውን ቅርጽ የያዘ ነው።

 

ሂሞግሎቢን

የስብ ውህደት ደግሞ በደማችን ሲለካ ትራይግሊሴራይድ ተብሎ የሚጠራው የሚከተለውን ይመስላል።

ትራይግሊሴራይድ

የነዚህን ውህዶች መጥን ስንመለከት ደግሞ፣ የውሃው ውህድ ካንድ የታይፕ ወረቀት ቅጥነት በሚሆን ወደ 350 ሚሊየኑን ማስቀመጥ ስንችል፣ በዚያው ስፋት ውደ 20 ሚሊየን ሂሞግሎቢን ማስቀመትጥ እንችላለን። ክብደተቸውን ስንመለከት ይውሃው ውህደት በአንድ ግራም ሰላሳ ሺህ ቢሊየን ቢሊየን (322 ዜሮ) ውህዶች ሲይዝ ዘጠኝ ቢሊየን ቢሊየን (918ዜሮ) ሂሞግሎቢን ውህዶችችን ማካተት ይችላል።

የደም ማነስ ሲጠረጠር በደማችን የሂሞግሎቢን መጠን የሚለካ ሲሆን፣ ኖርማል በሚሆንበት ጊዜ በአንድ የደም ጠብታ በአማካይ 7.5 ሚሊግራም (የአንድ ግራም አንድ ሺኛ) ሲገኝ፣ ይህም ወደ ስልሳ ሚሊየን ቢሊየን (616 ዜሮ) ውህዶችን ያካትታል።

በሰውነታችን የሚገኙ ውኡህዶችን ከላይ ባየነው መልክ የንጥረ ነገር ይዘታቸውንንና እንዲሁም ቅርጻቸውን በሚገባ የመረዳት አስፈላጊነቱን ደግሞ በሚቀጥለው ልጥፍ እንመለከታለን።


ረቡዕ 22 ሜይ 2024

ረቂቁ አቶም (ክፍል 3ሃ) - ሂወት ሰጭ አቶሙ ካርበን

 

19ኛው ክፍለ ዘመን በፊት ሂወት ያላቸው ፍጡሮች በልዩ ሂወት ሰጭ ሃይል አማካይነት ንጥረ ነገሮችን በማዋሃድ ኦርጋኒክ የተባሉ ውህዶችን ይገነቡ እንደነበረ ይታመን ነበር። ንጥረ ነገሮቹ መካከል ካርበን በዋነኛነት አስፈላጊ ሲሆን፣ በተጨማሪም ሃይድሮጅን፣ ናይትሮጅን፣ ኦክሲጅንና እንዲሁም አነስ ባሉ መጠኖች ሰልፈር፣ ፎስፎረስ እና ሌሎችም ይገኙባቸዋል። በጊዜው እነዚህ ኦርጋኒክ የተባሉ ውህዶች ሂወት ባለቸው ፍጡሮች ብቻ ሊሠሩና ከዚህ ውጭ ግን በተለመዱት የኬሚካል የማዋሃድ ዘዴዎች መሥራት እንደማይቻል ይታመን ነበር።

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1824 ፍሪድሪክ ሆለር የተባለ ሳይንቲስት ኦክዛሊክ አሲድ የተባለውንና እስከዚያ ድረስ እንደ ኦርጋኒክ ይታይ የነበረውን ውህድ በላብራቶሪ በመሥራት፣ እንዲሁም በ1828 ዩሪያን (አው የማዳበሪያው) በመስራቱ፣ እንዲሁም ከዚያ በኋላ የተለያዩ ሳይንቲስቶች ከነዚህም የበለጡ ውስብስብ የሆኑ ውህዶችን በላብራቶሪ በመሥራታቸው፣ ልዩ ሂወት ሰጭ ሃይል በፍጡርሮች ውስጥ የመገኘቱን ሃሳብ ውድቅ አድርገውታል።

ምንም እንኳ ካርበን የተለየ ነፍስ ሰጭ ሃይል ወይም ንጥረ ነገር ባይሆንም፣ ነፍስ ያላቸው የሚገነቡበት ውህዶች ሁሉ ካርበነን መሠረት ያረጉ ሲሆን፣ ካርበንም ለዚህ ተግባር ተስማሚ የሚያረጉት ልይ ባህርዮች አሉት። ከነዚህ ባህርዮች ዋናዎቹ ከሌሎች ንጥረ ነገሮች በቀላሉ ውህደት የመፍጠር ችሎታውና፣ የካርቦን አቶሞች እርስ በእርስ በመገጣጠም ረጅም ሰንሰለቶችንና ቀለበቶችን የመሥራት ችሎታው ይገኙባቸዋል። እንዚህ ካሮበንን መሠረት አርግው ሒውት ያላቸውን ሁሉ የሚገነቡት እነማን ናችው ብለን ብንጠይቅ፣ ከምንመገባቸው ይዘት በተያያዘ ስማቸው ሲጠራ የምንሰማው ካርቦሃይድሬት ቅባትና ፕሮቲን ሆንው እናገኛቸዋለን። ቀደም ባለ ልጥፍ ንጹህ ካርቦን በጥላሸት፣ በአልማዝ እንዲሁም በእርሳስና ባትሪ ድንጋይ ውስጥ ግራፋይት ተብሎ በሚጠራ መልኩ እንደሚገኝ ተመልክተናል። ይህ ራሱ ካርቦን ከሌሎች ንጥረ ነገሮችና እርስ በእርሱ በመዋሃድና በመደራጀት ሂወት ላላችው ሁሉ መሠረታዊ ሆኖ እናገኘዋለን! አንድ ሌላ እጅግ አስደናቂ አሁንም ካርበን ላይ የተመሠረተ ሒውት ባለችው ሁሉ የሚገኝ ውህድ መጥቀስ ይቀረናል። ይህም ዲኤንኤ ይተባለው ሲሆን በዘር የሚተላለፉ ባህረዮችን መረጃ በአቶሞቹ አወቃቀር የያዞ የምናገኘው ነው።

በዚህ ዓይነት አንድ ፍጡር የገነቡትን ውህዶችንና አቶሞችን ነጥለን የመለያየት ችሎታ ቢኖረን፣ የተለእያየ መጠን ሃይድሮጅን፣ ናይትሮጅንና፣ ኦክሲጅን ጋዞችን፣ እንዲሁም እንደፍጡሩ ዓይንት ይተለያየ መጠን ያልው ይጥላሸት መሰል ክምር እናገኛለን። እንዚህ ተናጠል ንጥረ ነገሮች ሂወት አልባ ከሆኑ ነገሮች ከምናገኛችው ምንም ልዩነት የላቸውም። ነገር ግን በተለያዩ ውህደቶችና መዋቅሮች ሲደራጁ፣ ሂወት ባላቸው ፍጡሮች የምንመለከታቸውን ባህርዮች ሲያመነጩ እንታዘባለን።

ስለ አቶምና ሒውት ይህን ያህል ካልን፣ በቀጣዩ ልጥፍ አቶሞችንና ውህዶችን ለመረዳት የሚያስችሉንን የምስል አይነቶች እንመለከታለን።


ዓርብ 18 ዲሴምበር 2020

የሳይንስና የሂሳብ ቁርኝት - ስለወረርሽኝ የሚነግረን

የሂሳብ ወይም ማትማቲችስ ከሳይንስ ጋር ከፍተኛ ጥምረት እንዳለው ብዙዎቻችን አንዘነጋም። ዘመናዊ ህክምናም ሳይንስ ላይ የተመሠረት እንደመሆኑ መጠን ብስፋት የሂሳብ ዘዴዎችን ይጠቀማል። ከህክምና ሳይንስ መካከል የወረርሽኝ ጥናትን ያካተተው ኤፒዴምዮሎጂ (Epidemiology) የተባለው ዘርፍን ስንመለከት ከሂሳብ ጋር ያለው ቁርኝት ከፋ ያእ ነው። ቀጥለን የዘንድሮውን የኮሮናቫይረስ ወረርሺኝም አስታከን፣ ሂሳብ በምን ዓይነት ወረርሺኝን ለመረዳት እንደሚያስችለን እንመልከት።

ለመነሻም ያህል ለአንድ ቀን ብቻ ህምም የሚያስከትል ተላላፊ በሽታን እንመልከት። በተጨማሪም በዚህ ህመም ከተያዘ ግለሰብ ጋር የሚገናኙ ሁሉ በበሽታው ይያዛሉ ብለን እናስብ። እያንዳንዱ ታማሚ ከሁለት ሰዎች ጋር ይገናኛል ብንል፣ ትንሽ ሂሳብ ሠርተን በየቀኑ የሚኖረውን የህመምተኛ ብዛት ማወቅ እንችላለን።

የመጀመሪያው ህመምተኛ የተያዘበትን ቀን 1 ብለን ብንጀምር፣ የህመምተኞቹን ብዛት ለማወቅ የፈለግንለት ከዚህ ቀን ጀምረን በመቁጠር፣ ከሱ ቁጥር ላይ አንድ እንቀንንሳለን። ቀጥለንም ሁለት ቁጥርን (እያንዳንዱ ህመምተኛ ለሁለት ሰዎችን ሰለሚያስተላልፍ) በዚህ ቁጥር መጠን በራሱ ስናባዛው፣ በዚያች ዕለት የሚኖሩትን የህመምተኞች ብዛት እናገኛለ። የበለጠ ግልጽ እንዲሆን ለምሳሌ በአሥረኛው ቀን ላይ የሚኖረውን የህመምኛ ብዛት ለማወቅ፣ ከአሥር ላይ አንድ ስንቀንስ ዘጠኝ ይሆናል፣ ሁለትን ዘጠኝ ጊዜ በራሱ ስናባዛ፣ ማለትም ሁለት ሲባአዛ በሁለት ሲባአዛ በሁለት ሲባአዛ በሁለት ሲባአዛ በሁለት… ዘጠኝ ጊዜ፣ 512 ሰው ይሆናል ማለት ነው።

10 – 1 = 9

2 X 2 X 2 X 2 X 2 X 2 X 2 X 2 X 2 = 512

ይህን ሂሳብ አንድ ህመምተኛ ሶስት ሰው ያገኛል ብለን ብንሠራው 10ኛው ቀን ላይ አስደንጋጩ አስራዘጠን ሺህ ስድስት መቶ ሰማኒያ ሶስት (19683) ብዛት ያህል ህሙማን የኖሩናል። ወይም በሂሳብ ቋንቋ አጻጻፍ የብዜቱን ለክ ከፍ በማድረግ፤

39 = 19683


አራት ሰው ቢያገኝ 10ኛው ቀን ላይ፤

49 = 262144 ህመምተኞች ይኖራሉ

በዚህ አይነት ቀለል ያለ ሂሳብ አሠራር ስለ የወረርሺኝ ስርጭት ግምት ማግኘት የሚቻል ሲሆን ካዕውነታው ጋር ለማዛመድ ግን ሌሎች ግብዓቶችን ማካተት ይኖርብናል። ከላይ የተመለከትነው አንድ ህመምተኛ ከሚገናኛችው ለሁሉም ህመሙን እንደሚያስተላልፍና ህመሙም የአንድ ቀን ቆይታ ብቻ ይኖረዋል ብለን ተነሳን። በተግባር ስናይ ግን የተላላፊ በሽታዎች ከህመምተኛው ተነስተው ወደሌላው የመተላለፍ አቅማቸው የሚለያይ ሲሆን፣ በተለያዩ ምክኒቶች ሳቢያ ግንኙነት ካላችው አንድም ግለሰብ ሳያስቀር የሚተላለፍ ተላላፊ ህመም አይኖርም። ተላላፊ ህመሞች አንድ ህመምተኛ ላይ የሚቆዩትና ሊስተላለፉ የሚችሉበትም ወቅት ከላይ እንደተመለከትነው አንድ ቀን ብቻም አይሆንም። እንዚህን ግብዓቶች ስናካትት በየቀኑ ይሚኖሩትን ህመምተኞች ብዛት ለማወቅ መሥራት ያለብን ሂሳብ የበለጠ ውስብስብ ይሆናል። በአጭሩ ግን አንጋፋው አይዛክ ኒውተን በቀረጸው ካልኩለስ በተባለ የሂሳብ ስልት በመጠቀምና በኮምቲዩተር በመታገዝ፣ ከተጋላጭ ህዝቡ በየቀኑ በህመሙ የሚያዘውን ክፍል ምን ያህል እንደሚሆን መገመት ያስችለናል።

ቀጥለንም ኮሮናን ወይም Covid 19ኝን ስንመለከት እስካሁን በተለያዩ ሃገራት ባለን መረጃ አንድ ታማሚ በአመካይ ከ 2 እስከ 6.6 ለሚደርሱ ሰዎች እንደሚያስተላልፍና የህመሙም ቆይታ ጊዜ 14 ቀን ያህል ሲሆን፣ ከ እንዚህ ቁጥሮች ተነስተን ህመሙ በህብረተሰቡ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በየቀኑ ሊኖሩ የሚችሉትን ህመምተኞች ብዛት ስንመለከት እንደሚከተለው ይሆናል።

በአነስተኛው ብንሄድና አነድ ግለሰብ በህመሙ ወቅት ለሁለት ሌሎች ሰዎች ቢያስተላልፍ፣ ከፍተኛውን የህመምተኛ ብዛት - ከተጋላጭ ህብረተሰቡ 16 ከመቶ የሚሆነውን በ160ኛው ቀን አካባቢ ሆኖ እናገኘዋለን። ለማሳሌ ያህል የአዲስ አባባ ህዝብ ሁሉ ተጋላጭ እንደሆን ብናስብና ብዛቱም 5 ሚለየን በሆን፣ 16 ከመቶ ያህሉ 800 ሺህ ይሆናል ማለት ንው። በከፍተኝው 6.6 ከሄድን ደግሞ በ35ኛው ቀን ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ህመምተኞች የምናይ ሲሆን ከህብረተሰቡ 57 ከምቶ ወይም ከ5 ሚሊየኑ 2.85 ሚሊየን ታማሚዎች የኖራሉ (ትንሽ በዛ)

ሂሳቡ የሚሰጠንን ትንበያ ከመረጃው ጋር ስናነጻጽር፣ የመጀመሪያው ህመምተኛመጋቢት 2012 መገኘቱ ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ ከተመረመሩት መሃል ከፍተኛ ከፍሉ ማለትም ከ10 እስከ 20 በመቶ ህመሙ የተገኘባቸው ወደ 140 ኛው ቀን አቅራቢያ ነኅሴ ውስጥ ሆኖ እንመለከተዋለን። ይህም ከመጀመሪያ ትንበያችን ብዙ አይራራቅም። በአንድ ቀንም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህሙማን የተገኙት በዚሁ ወር ላይ ነው (1829 ህመምተኞች)። በጠቅላላው በዚህ ወቅት በምርመራ የተገኙት ህሙማን ቁጥር 15ሺህ ሲሆን፤ በትንበያው መሠረት ግን ነኅሴ ላይ ወደ 800 ሺህ ህሙማን መኖር እንደነበረባቸው ያመለክታል። ይህም የሚጠቁመን ከህሙማን መካካል እጅግ በጣም ጥቂቱን ነው በምርመራ እያገኘን ያለነው። እንዚህንም ብቻ በለይቶ ማቆያ ከተቀረው ህብረተሰብ መለይት ስርጭቱን ለመግታት ያለው ጠቃሚነቱን አጠያያቂ ያረገዋል።

ሌላው ከሂሳቡ የምናገኘው ትንበያ አሁን በታህሳስ ውር 2013የህመምተኞት ብዛት ከህዝቡ 0.3 ከመቶ መሆን እንዳለባቸው ሲሆን፣ ነገር ግን ሰሞኑን ያሉ መረጃዎች ከሚመረመሩት መካከል ከ5 እስከ 10 ከመቶ ያሉት ህመምተኞች እንደሆኑ ያመለክታል። መለስ ብለን ስንመለከት ምናልባት ከነኅሴ 2012 ጀምሮ ባለው ጊዜ ከተመረመሩት ከ5 እስከ 10 ከመቶ ህመሙ እንደተገኘባቸው የምናይ ሲሆን ይህ ቁጥር በጣም ከፍ ወይም ዝቅ የማለት ዝንባሌ አላሳየም። ይህም የሚነግርን በአማካይ አንድ ህመምተኛ በህመሙ ዋቅት ለአንድ ግለሰብ ብቻ እያስተላለፈ እያለ መሆኑን ነው። ቀድም ብለን ካየነው በአማካይ አንድ ህመምተኛ ለሁለት ግለሰብ ከማስተላለፍ ወደ አንድ ግለሰብ ብቻ ማስተላለፍ መቀነሱና በትንበያው መሠረት ወረርሽኙ ወደመጠናቅ አለመጠጋቱ (የሂሳቡ ወደተነበየው 0.3ከመቶ አለመውረዱ) ማናልባት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተወሰዱት እርምጃዎች ማለትም ርቅትን የመጠበቅና ማስክን የመልበስ፣ ተጋላጩ ወገን ሁሉ በህመሙ ሳይያዝ፣ የስርጭቱ ፍጥነት መቀነሱንና ከላይ እንደጠቀስነው አንድ ህመምተኛ ለአንድ ሌላ ግለሰብ ብቻ እያስተላለፉ ራሱን በመተካት ለይ እንዳለ መሆኑን መገመት የቻላል። ይህም ከሆነ ግን ትንሽ ጥንቃቄያችንን ከዘነጋን ወረርሽኙ መለሶ ሊያገረሽ እንደሚችል ማሰብ ይኖርብናል።

በቀጣይ ልጥፍ ከሌሎች በዓድገት የበለጸጉ ሃገራት ሲነጻጸር የኮሮና ህመም በሃገራችን የፈጠረው አስከፊነት አነስተኛ ይሆነበትን ምክኒያት አሁንም ከሂሳብ ጋር በማያያዝ ለመግለጽ እሞክራለሁ።

ይልጥፉ መረጃዎች የተገኙበት፤ Our World in Data፣ worldometer

ሂሳቡን የበለጠ ለመረዳት፤ Spread of Disease

ሂሳቡን ለመሥራት ሶፍውዌር፤ RKWard


ረቡዕ 20 ማርች 2019

ከሳይንስ አድማስ (02-2011) - ሳይንስ ሶሺያል ሚዲያና ፖለቲካ



ሶሺዮሎጂ (Sociology) - የህብረተሰብ ጉዳዮችን በሳይንሳዊ አካሄድ ማጥናት ሲሆን፣ ከሶሺያል ሳይንሶቹ (ታሪክ፣ ጂዮግራፊ፣ ፖሊቲካል ሳይንስ፣ ምጣኔ ሃብት ጥናት ወዘተአንደኛው ዘርፍ ነው። በህብረተሰብ ውስጥ የሚታዩ ግንኙነቶች፣ ባህሎች፣ ባህሪዮችን በዚህ መልክ በማጥናት የሚገኙት መረጃዎችም ፖሊሲ ለማርቀቅና ለማቀድ ጠቃሚ ግባዓት ሊሆኑ ይችላሉ። ባአሁኑ ውቅት ደግሞ ድረ መረብ ላይ ያሉ ሶሺያል መዲያ (Social Media) በሚሊዮን የሚቆጠሩ የህዝብ አስተያየቶችን፣ ሃተታዎችን፣ አመለካከቶችን በኮምፒዩተር እገዛ አጣርቶ ለመመርመር አመቺ በሆነ መልኩ በማስቀመጥ፣ ከዚህ ቀደምሊታሰብ ባልተቻለ መልኩ ለሶሺዮሎጂ ተመራማሪውች ትልቅ ዕድል ፈጥሯል። ይህንንም ዕድል በመጠቀም በቱዊተር (Twitter) የሚተላለፉ ሃሰተኛ መርጃ አሰረጫጭትን በተመለከተ ሶስት ተመራማሪዎች (ቮሱጊ፣ ሮይና አራል የተባሉያደረጉትን ጥናት ውጤት በሳይንስ ምጽሄት (Science 359, 9th March, 2018) ይፋ ተደርጓል። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2017 .በቱዊተር ይተላለፉ ዕውነተኛና ሃሰተኛ ልጥፎችን ተመለከተዋል። በዚህም ወቅት በሶስት ሚሊየን ሰውች አራት ተኩል ሚሊየን ጊዜ የተላለፉ ልጥፎችን መርምረዋል። የእውነተኝነት ውይም ሃሰተኝነት ይዘታቸውን ለመለየት ስድስት የተላያዩ ገለልተኛ አጣሪ አካሎችን ግምገማ ተጠቅመዋል። በዚህም ጥናት የታየው ሃሰተኛ ይዘት ያላቸው ልጥፎች ከእውነተኞቹ በበለጠ ፍጥነትና ስፋት መሰራጨታቸውን አረጋግጠዋል። ከዚህም በተጨማሪ የልጥፎቹን መልዕክት ሲመለከቱ የፖለቲካ የዘት የያዙ ሃሰተኛ ልትፎች ከሌሎቹ ስለሽብር፣ ተፈጥሮ አደጋ፣ ሳይንስ፤ የከተማ ወሬና ስለንግድ መረጃ የዘት ካላቸው የሃሰተኛ ልጥፎች ሲነጻጸር ከሁሉም በበለጠ ደረጃ መሰራጨታቸውን አረጋግጠዋል። በሶሺያል ሚዲያ የሚተላለፉ መልዕክቶች ህብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ተዕጽኖ ሊኖራቸው እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ለምሳሌ ያህል ፕረዚደንት ኦባማ በፈንጂ ቆስለዋል በሚል ሃሰተኛ መልዕክት በስቶክ ግብይት (Stock Market) ላይ በነበረው ተዕጽኖ መቶ ሰላሳ በሊየን ዶላር የሚገመት ኪሳራ አድርሷል። በቅርብ ጊዜ ቢቢሲ የዘገበውም በሜክሲኮ ሃገር በዋትሳፕ (WhatsApp) ልጆችን አግትዋል ተብሎ በተላለፈው ሃሰተኛ መረጃ ምክኒያት በተቀሰቀሰ ቡድን ሁለት ግለሰቦች በእሳት ተጋይተው ሂወታቸው ሊያልፍ ችሏል። አንዳንድ ጊዜ በተለያየ ሃገር በሚኖረው የፖለቲካ አለመረጋት ወቅትም በሶሺያል ሚዲያ የሚሰራጭ ሃሰተኛ መረጃ ሊያደርስ የሚችለውን ቀውስ ስናስብ ምናልባት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል ብንል አይፈረድብንም።